የቡና ፍሬዎች
12,00 ዩሮ
1 ኪ.ግ. 12,00 ዩሮ
ግብዓቶች: የቡና ቸርች
የአመጋገብ መረጃ በ100 ግራም
ኃይል፡ :2 ኪ.ካል
ስብ፡ :0.1 ግ
ካርቦሃይድሬት፡ :0 ግ / ከእነዚህም ውስጥ ስኳር፡ 0 ግ
ፋይበር፡ :3.6 ግ
ፕሮቲን፡ :0.1 ግ
ጨው፡: 0 ግ
የቡና ፍሬዎች
የቡና ስም የመጣው ከመነሻ ቦታው ከሆነው ከፋ ከሚባለው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ከሚገኝ የኣንድ አካባቢ ስም ነው። “Coffee Bean” የሚለው ቃል ከ“ከፋ ቡና” የመጣ የእንግሊዝኛ አጠራር እንደሆነ ይታመናል። ባህላዊው የቡና ሥነ-ሥርዓት በኢትዮጵያም ሆነ በኤርትራ ዋና ባህላዊ ልማድና አስፈላጊ ማህበራዊ እሴት ነው።
ቡናን ለማዘጋጀት በባህሉ መሠረት አረንጓዴ የቡና ፍሬዎች በውኃ ይታጠባሉ፣ ከዚያም በትንሽ የከሰል እሳት ላይ በምጣድ ትኩስ ሆነው ይቆላሉ። ቡናው ከተቆላ በኋላ የጪሱ ሽታ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ለሚቀርበው ጣፋጭ ቡና እንደ መጀመርያ ጣእም ይታያል።
ከዚያ በኋላ የቡና ፍሬዎቹ በእጅ ይፈጫሉ፣ ከዚያም “ጀበና” በሚባል ከልዩ ሸክላ በተሠራ ባህላዊ የቡና ማፍያ ውስጥ ይገባሉ። ውኃ ተጨምሮባቸውም በክፍት እሳት ላይ ይፈላሉ። ቡናው በተገቢው ጊዜ ከፈላ በኋላ፣ ጀበናው ቡናው እንዲረጋጋ እና ቅሪቱ ወደ ታች እንዲወርድ ለአንድ ወይም ለሁለት ደቂቃ ከእሳት ላይ ወርዶ ይቀመጥና ዝግ እንዲል ይደረጋል። መልካም ቡና!


